የባሃኢ አስተዳደር ስርዓት በመመካከር ላይ የተመሰረተ ነው፡፡የምክክር መርህ ከመለኮታዊ የእምነት ሥርዓቶች ውስጥ አንዱ ነው። በምክክር ውስጥ የሚሳትፉ አባላት፡ በፍፁም ፍቅር፣ ስምምነት እና ቅንነት መመካከር ይኖርባቸዋል። ተቋማት በቻ ስይሆኑ፡ በእለት ተእለት የተለመደ ጉዳዮቻቸውም ቢሆን፣ የህብረተሰቡ አባላት በሁሉም ጥረቶቻቸው ውስጥ መመካከርን መልመድ ይኖርባቸዋል።
ለሚመካከሩ ሁሉ መሠረታዊና አስፈላጊ ነገሮች የሃሳብ ቀናነት፥ የመንፈስ ንጽሕና፥ ከሁሉም የግል ፍላጎቶች ርቆ የእግዚአብሕርን ብቻ መከተል፥ በመለኮታዊ መዓዛው መማረክ፥ በምዕመናኑም መካከል ትሕትናና ዝቅተኝነትን ማሳየትና እግዚአብሔርን በማገልገል ላይ በሚደርሰው ረጅም ሥቃይና ችግር መታገስ ናቸው።
በዚህ ዘመን የጉባኤዎች መመካከር አንገብጋቢና እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። ለእነርሱም መታዘዝ አስፈላጊና ግዴታም ነው። የተቋም አባሎቹ አንዳች ቅሬታና አለመግባባት በማይፈጠርበት መንገድ መነጋገርና መወያየት አለባቸው። ይህም የሚሆነው እያንዳንዱ አባል ሃሳቡን በሙሉ ነፃነት አቅርቦ ምክንያቶቹን በግልጽ ሲደረድር ነው። ማንም ሰው ሃሳቡን ቢቃወም ጉዳዩን አጣርተው እስከተወያዩበት ድረስ እውነተኛው መንገድ ስለማይገለጥ መቀየም የለበትም። የእውነት ብልጭታ የሚታየው ልዩ ልዩ ሃሳቦች ከተጋጩ በኋላ ነው። ከውይይቱ በኋላ አንድ ሃሳብ በሁሉም ከተደገፈ መልካም ነው፤ ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ባይሆንና ልዩነት ቢፈጠር የድምፅ ብልጫ ያገኘው ሃሳብ መጽደቅ አለበት።
“የመጀመሪያው ሁኔታ በጉባኤው አባሎች መካከል ፍጹም ፍቅርና ስምምነት መፍጠር ነው። የአንድ ባሕር ውሃ፥ የአንድ ወንዝ ፏፏቴዎች የአንድ ሰማይ ከዋክብት፥ የአንድ ፀሀይ ብርሃን፥ የአንድ ቦታ ዛፎች የአንድ ተክል ሥፍራ አበቦች በመሆናቸው የልዩነትን መንፈስ ማስወገድና የእግዚአብሔርን አንድነት ማሳየት አለባቸው። ፍጹም አንድነትና ስምምነት ከሌለ ያ ስብሰባ መበተን፥ ጉባኤውም እንደሌለ መቆጠር አለበት። “ሁለተኛው ሁኔታ ወደ ስብሰባው በሚመጡበት ጊዜ ፊታቸውን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መመለስና ከእግዚአብሔርም ዕርዳታን መጠየቅ አለባቸው። ... ውይይቱ ነፍስ የምትዳብርበት፥ ሕፃናት የሚማሩበት፤ የድሆች ችግር የሚቃለልበት፤ በዓለም ያሉ በማንኛቸውም ክፍል የሚገኙ ድኩማን የሚረዱበት፤ ለሰው ሁሉ ችሮታ የሚደረግበት፤ የእግዚአብሔር መዓዛ የሚሰራጭበትና ቅዱስ ቃሉ የሚስፋፋበትን የመሳሰሉ መንፈሳዊ ጉዳዮችን የሚመለከት መሆን አለበት። እነዚህን ሁኔታዎች ለመሟላት ከቻሉ የመንፈስ ቅዱስ ፀጋ ይወርድላቸውና ጉባኤው የመለኮታዊ ቡራኬ ማዕድ ይሆናል። የሰማይ መላእክት ለእርዳታ ይደርሱላቸዋል። በየዕለቱም በአዲስ መንፈስ ይሞላሉ።” የባሃኢ ጽሑፎች
Interesting blog? Like it on Facebook, +1 on Google, Tweet it or share this article on other bookmarking websites.