የኢትዮጵያ ባሃኢዎች
  • የባሃኢ ትምህርቶች
    • አምላክና ሐይማኖቶች
    • የአምላክ መልእክተኞች
    • የባሃኢ ትምህርቶች
    • ህግጋቶችና ደንቦች
    • አስተዳደር
  • ማህበረሰባዊ ተሳትፎ
    • ማህበረሰብ ግንባታ
    • የወጣቶች እንቅስቃሴ
  • የባሃኢ ማህበረሰብ
    • የኢትዮጵያ ባሃኢዎች
    • የአለም ዓቀፍ ማህበረሰብ
    • የባሃኢ ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ - አዲስ አበባ ጽ / ቤት
    • ባሃኢዎችን እናስተዋውቃችሁ
  • የባሃኢ መጽሐፍት
    • ቅዱሳን ጽሑፎች
    • ሌሎች
  • ለበለጠ መረጃ
    • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች
    • መልእክት ይላኩልን
    • ቪዲዮዎች
  • ENGLISH

የጋራ ፀሎተ-አምልኮ

 

ከባሃኢ ሃይማኖት ዋና ዋና መርሆዎች አንዱ ከሁሉም ሃይማኖት ተከታዮች ጋር በወዳጅነት መቀላቀል ሲሆን፤ የዚህም የተግባር መገለጫ የሁሉንም የሃይማኖት ተከታዮች የሚያሳትፉ የጋራ ፀሎተ አምልኮ ክፍለ-ጊዜዎችን ማካሄድ ነው። ባሃኢዎች የጋራ ፀሎት የአንድ ማህበረሰብ ህብራዊ አብሮ መኖር ዋነኛ መገለጫ መሆኑን በመረዳት ይህ በሁሉም ቦታ እንዲተገበር ሁኔታዎችን ያመቻቻል። በዚህ የፀሎት ክፍለ-ጊዜም ሁሉም እንደየእምነቱ ፀሎቱ እንዲያደርግ፥ ከየቅዱሳን መፅሀፎቹ እንዲያነብ ይበረታታል።

ይህ ክፍለ-ጊዜ በየቤቱና እንደየሁኔታው በየአመቺ ቦታው የሚካሄድ ሲሆን ሁሉም በጋራ ሃላፊነት የሚወስዱበት እንቅስቃሴ እንጂ የግለሰብ ወይንም የአንዱ ሃይማኖት የበላይነት የሚኖረው አይደለም። የዚህ ክፍለ-ጊዜ ዓላማ በሁሉም ሰዎችና ሃይማኖቶች መካከል አንድነትን ለማጠንከር፥ መቻቻልን ለማጎልበት፥ ሰላማዊ ህይወትን ለመምራትና ጥላቻን ለመቋቋም ማስቻል ነው።

ይህን እንቅስቃሴ በአገራችን በተለያዩ የክልል ከተሞች መንደሮች ፥ ሰፈሮችና ቦታዎች እየተተገበረ ይገኛል። በዓለም ዙሪያ በተለያዩ ሃይማኖቶች ተከታዮች መካከል ካለው መቃቃርና የእርስ በእርስ ጥላቻ አንፃር፥ የተለያዩ ሃይማኖት ተከታዮች በአንድ መንፈሳዊ ማእድ ዙሪያ በፍቅርና በወዳጅነት መንፈስ ሲፀልዩ ማየት በእውነቱ ልብን በተስፋ የሚሞላ ነው።

ለበለጠ መረጃ፤ www.bahai.org

Interesting blog? Like it on Facebook, +1 on Google, Tweet it or share this article on other bookmarking websites.

የማህበረሰብ ግንባታ

  • የህፃናት ትምህርት
  • የማህበረሰብ ግንባታ
  • የታዳጊ ወጣቶች ፕሮግራም
  • የጋራ ፀሎተ-አምልኮ
  • የጥናት ክበባት
  • Follow via Facebook
  • Follow via Youtube
unity

© 2023 የኢትዮጵያ ባሃኢዎች

Go Top