እ.ኤ.አ. በ 2019 በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች በ 1844 የሰው ልጅ ወደ አዲስ ዘመን እየገባ መሆኑን የገለፀው የእግዚአብሔር መልእክተኛ ባብ የተወለደበትን 200ኛ የልደት ክብረ በዓል አከበሩ ፡፡ ባብ ፍትህ እና ዘላቂ ሰላም ለመፍጠር ዓለም ሁሉ አንድ የሚያደርግበትን አዲስ ትምህርት ከእግዚአብሔር እንዲቀበሉ ሰዎችን ያዘጋጃቸው ነበር ፡፡
ባብ ለዚህ ዘመን መለኮታዊ ትምህርት ገላጭ ለሆነው ለባሃኡላህ መንገድ ጠረገ፡፡ የባሃኡላህ አንድነት እና መንፈሳዊ እድሳት አስተምህሮዎች የባሃኢ እምነት መሰረት ናቸው ፡፡ የባሃኡላህ 200ኛ የልደት ክብረ በዓል በ 2017 የተከበረው ፤ ለሁለት ዓመት የደስታ መታሰቢያ በመጀመር ነበር ፡፡
ምንም እንኳን ብዙዎች የእነዚህን ሁለት መለኮታዊ መልእክተኞች ታሪክ ገና ያልሰሙ ቢሆንም ፣ የበለፀጉ መንፈሳዊ እና ማህበራዊ ትምህርቶቻቸው ድምፅ በዓለም ዙሪያ ያስተጋባሉ ፡፡
Interesting blog? Like it on Facebook, +1 on Google, Tweet it or share this article on other bookmarking websites.