የኢትዮጵያ ባሃኢዎች
  • የባሃኢ ትምህርቶች
    • አምላክና ሐይማኖቶች
    • የአምላክ መልእክተኞች
    • የባሃኢ ትምህርቶች
    • ህግጋቶችና ደንቦች
    • አስተዳደር
  • ማህበረሰባዊ ተሳትፎ
    • ማህበረሰብ ግንባታ
    • የወጣቶች እንቅስቃሴ
  • የባሃኢ ማህበረሰብ
    • የኢትዮጵያ ባሃኢዎች
    • የአለም ዓቀፍ ማህበረሰብ
    • የባሃኢ ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ - አዲስ አበባ ጽ / ቤት
    • ባሃኢዎችን እናስተዋውቃችሁ
  • የባሃኢ መጽሐፍት
    • ቅዱሳን ጽሑፎች
    • ሌሎች
  • ለበለጠ መረጃ
    • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች
    • መልእክት ይላኩልን
    • ቪዲዮዎች
  • ENGLISH

የወጣቶች እንቅስቃሴ

 

“ወጣቶች አለምን ማንቀሳቀስ ይችላሉ!” 

የመጡበት ማህበረሰብ ሁኔታ ምንም አይነት ይሁን ወጣቶች መንፈሳዊና አዕምሯዊ እድገትንና ለሰው ዘር ብልፅግና አስተዋእፆ ማበርከትን ይመኛሉ። ብዙ አስደናቂ ኃይሎች አላቸው። እነዚህን ኃይሎች በተገቢው ሁኔታ አቅጣጫ ማስያዝ አስፈላጊ ጉዳይ ነው። በተሳሳተ መንገድ የተመሩ እንደሆነ አልያም በሌሎች አግባብ ባልሆነ ሁኔታ መጠቀሚያ የሆኑ እንደሆነ ብዙ ማህበራዊ ቀውሶቹን ሊያስከትሉ ይችላሉ።

ወጣቱ ትውልድ በተወሰኑ ባህሪያት ተለይቶ ይታወቃል። ህይወታቸውም በተለያዩ ሃይሎች የተቀረፀ ነው። ብዙዎች ወጣቶች በተለያዩ የትምህርት ደረጃ በማለፍ እንዲሁም በቤተሰብና በማህበረሰብ ህይወት አልፈው ለጎልማሳነት ተግባራት ማለትም ለትዳርና ለስራ በመዘጋጀት ላይ ያሉ ናቸው። ለአንዳንዶቹ ደግሞ የወጣትነት ህይወት ከእነሱ በእድሜ በጣም የበለጡ ሰዎች ሊሰሯቸው የሚገባ የስራ ሃላፊነቶች የተጣሉባቸው ሊሆኑ ይችላሉ። እንዲሁም የቤተሰባቸው ህልውና በእነርሱ ትከሻ ላይ ያረፈ ይሆናል። ተወላጅነታቸውም ከዓለም ትንሹ ገጠር መንደር እስከ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ነዋሪዎችን የያዙ ትልልቅ የከተማ ማእከሎች ውስጥ ባሉ ሰፈሮች ድረስ የተለያዩ ናቸው።

የባሃኢ ፅሁፎች እንደሚገልፁት በዓለም ላይ “የጋራ ደህንነትን ለማምጣት ከሚደረግ ግልጋሎት የበለጠ” የተከበረ ተግባር እንደሌለና “መነሳትና ብዙሃኑን ለማገልገል በሙሉ ሃይላቸው ራሳቸውን ማትጋታቸው” መሆኑን ይገነዘባሉ። ለማህበረሰቡ የሚደረግ ከእኔነት የፀዳ አገልግሎት ግለሰባዊ እድገትና ለማህበረሰብ መሻሻል አስተዋፅኦ የማበርከት አቅምን ማጎልበት ያስችላቸዋል። “ምክንያቱም “ለሰው ልጅ የሚሰጥ አገልግሎት ለአምላክ የሚሰጥ አገልግሎት ነው።” ተሰጥኦአቸውንና ችሎታዎቻቸውን ማህበረሰቡን ወደተሻለ ደረጃ ከፍ እንዲል ካዋሉ እነሱ “የፍጥረት ዓለም የሰላምና የመረጋጋት ምክንያት ይሆናሉ።” የእለት ተዕለት እንቅስቃሴዎቻቸውን በልግስና የመስጠት መንፈስ ሲያላብሱና ለሌሎች ደህንነት ለበጎ ፈቃደኝነት ሲሰሩ የአምላክን እርዳታና ማረጋገጫዎች ይስባሉ።

ለማህበረሰብ ደህንነት አስተዋዕፆ የማድረግ ታላቅ ሃላፊነትን የተጋፈጠው የአሁኑ ወጣት ትውልድ ነው። ከዚህም በተጨማሪ በማህበረሰቡ ውስጥ ከእነሱ በእድሜ ለሚያንሱት ወጣቶች የአዲሱ ስልጣኔ ገንቢዎች ለመሆን የሚያስችላቸውን መንፈሳዊና አእምሯዊ ሃይሎች ለመቀዳጀት የሚያስችሏቸውን ምቹ አካባቢዎች (ኢነቫይሮመንት) የማመቻቸቱ ሃላፊነትም በእነሱ (በአሁኑ ወጣት ትውልድ) ላይ የተጣለ ነው። ሃላፊነቱ በእርግጥ እጅግ ትልቅ ነው። እራሳቸውን ከጎጂ ሃይሎች ለመመከት ፥ ወጣቶች በአምላክ የማይቀር እርዳታ ላይ እምነታቸውን ሊያሳድሩ ይገባል።

READ MORE: http://www.bahai.org/

Interesting blog? Like it on Facebook, +1 on Google, Tweet it or share this article on other bookmarking websites.

የማህበረሰብ ግንባታ

  • የህፃናት ትምህርት
  • የማህበረሰብ ግንባታ
  • የታዳጊ ወጣቶች ፕሮግራም
  • የጋራ ፀሎተ-አምልኮ
  • የጥናት ክበባት
  • Follow via Facebook
  • Follow via Youtube

ወጣቶች በማህበረሰብ ግንባታ ላይ እንዴት መሳተፍ ይችላሉ?

  • ህፃናትን በማስተማር

    የባሃኢ ሃይማኖት ሕፃናት የማሕበረሰቡ እንቁ እንደሆኑ ያምናል። በእነርሱ ውስጥ የወደፊቱ መልካም ተስፋ ተደብቆ ይገኛል። ይህ መልካም ተስፋ እውን እንዲሆን ግን ሕፃናትን በመንፈሳዊ ሕይወት ተንከባክቦና ኮትኩቶ ማሳደግ ያሻል።

  • የማህበረሰብ የጋራ ፀሎትን በማካሄድ

    ከባሃኢ ሃይማኖት ዋና ዋና መርሆዎች አንዱ ከሁሉም ሃይማኖት ተከታዮች ጋር በወዳጅነት መቀላቀል ሲሆን፤ የዚህም የተግባር መገለጫ የሁሉንም የሃይማኖት ተከታዮች የሚያሳትፉ የጋራ ፀሎተ አምልኮ ክፍለ ጊዜዎችን ማካሄድ ነው።

  • የታዳጊ ወጣቶች ክፍለ ጊዜዎችን በማካሄድ

    በየታዳጊ ወጣቶች የትምህርት ፕሮግራም ውስጥ የሚሳተፉት እድሜያቸው ከ12 እስከ 15 ዓመት የሆኑ ልጆች ናቸው።

  • የጥናት ክበባትን በመክፈት

    የጥናት ክበቦች በቤት ውስጥ ወይንም እንደሁኔታው በሚመች ቦታና አካባቢ ቁጥራቸው ለመወያየት በሚመች መልኩ የሚወሰን ጎልማሶች በሳምንት የሚፈልጉትን ቀን ያህል ወስነው የሚወያዩብትና የሚያጠኑበት መድረክ ነው።

© 2023 የኢትዮጵያ ባሃኢዎች

Go Top