የባሃኢ ሃይማኖት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ሳብሪ ኤሊያስ በሚባሉ ግብፃዊ አማኝ አማካኝነት ነው። እኝህ ሰው በወጣትነታቸው እ.ኤ.አ 1933 ዓ.ም ያለምንም ቅድመ ዝግጅት ፣በውስን አቅማቸውና የኢትዮጰያን ቋንቋዎችን ባለማወቃቸው ሳይገቱ የባሃኢ ሃይማኖትን ለማስተማር ወደ ኢትዮጵያ መጡ።
በልብስ ስፌት ስራም መተዳደር ጀመሩ ። ጎን ለጎንም ሃይማኖቱን ማስተማር ጀመሩ። ከብዙ ጥረት፥ ልፋትና ፈተናም በኋላ አንዳንድ ኢትዮጵያን ሰዎች ሃይማኖቱን መቀበል ጀመሩ። ከዚያም የባሃኢ ሃይማኖት የአስተዳደር ተቋም የሆነውን የአካባቢ መንፈሳዊ ጉባዔ ለመጀመሪያ ጊዜ ለማቋቋም አስቻሉ።
ከሳብሪ ኤሊያስ ታላቅ ስኬት መካከል “ባሃኡላህና አዲሱ ዘመን” የተሰኘውን መፅሀፍ በ1934 እ.ኤ.አ ወደ አማርኛ ለማስተርጎምና ማሳተም መቻላቸው ነው። የመፅሀፉም ቅጅ በጊዜው ለነበሩ ቤተ መጽሃፍቶችና ለዓለም ዙሪያ ለሚገኙ ባሃኢዎች ተሰራጭቷል። በ1936 እ.ኤ.አ የመፅሃፉ ቅጂ በወቅቱ የኢትዮጵያ መሪ ለነበሩት ንጉስ ሃይለስላሴ እየሩሳሌም በነበሩበት ወቅት ወ/ሮ ሎሮል ስቸፐፍሎቸር በተባሉ ካናዳዊ ባሃኢ አማካኝነት ተሰጥቷቸዋል። ተጨማሪ ያንብቡ
Interesting blog? Like it on Facebook, +1 on Google, Tweet it or share this article on other bookmarking websites.